Monday May 21, 2012
  • Ethiopian Defence Forces
  • Ethiopian Defence Forces
  • Ethiopian Defence Forces
  • Ethiopian Defence Forces
  • Ethiopian Defence Forces
  • Ethiopian Defence Forces
  • Ethiopian Defence Forces
Home
News Feeds:

የኤ.ፌ.ዲ.ሪ. መከላከያ ሚኒስቴር ራእይ፡-

ለህገ መንግስታዊ ሰርዓቱ ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ አገራችንና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን ከማንኛውም አደጋ በአስተማማኝነት፣ የሚጠብቅ ጤንነቱ የተጠበቀ፣ ብቃትና ዲሲኘሊን ያለው፣ ለአገራችን ህዝቦች እኩልነትና መፈቃቀድ ተምሳሌት የሆነ፣ የህዝብ አመኔታና ፍቅርን የተጎናፀፈ፣ በአህጉራዊና አለም አቀፋዊ ሰላም ጥበቃ ውስጥ ተገቢውን ሚና የሚጫወት ጠንካራና ዘመናዊ የመከላከያ ሃይል መገንባት፡፡


የኤ.ፌ.ዲ.ሪ. መከላከያ ሚኒስቴር ተልዕኮ፡-

1. ሀገራችንና ሕገ-መንግስታችን ከውጭ ወራሪ ሀይሎች፣ ሽብርተኝነትና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ሃይሎች በአስተማማኝ በመከላከል የሀገራችን ሰላም፣ ፈጣን ልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እንቅስቃሴ ያለ እንቅፋት እንዲቀጥል ማድረግ፤


2. አግባብ ያላቸው የክልል መስተዳድር የደህንነትና የፀጥታ መዋቅሮችን የደህንነትና የፀጥታ አቅማቸውን መገንባትና ተቀናጅቶ መስራት፤


3. የሀገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ የህዝብና የመንግስት የልማት ተቋማትንና አውታሮችን ከማንኛውም ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች መከላከልና ማዳን፤


4. ሀገራዊ ደህንነትን በማረጋገጥ በከባቢያዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የሰላም ተግባራት ላይ በብቃት መሳተፍ፤

 

የኤ.ፌ.ዲ.ሪ. መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-

1.    ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር

2.    ምን ጊዜም የተሟላ ስብእና

3.    ያልተሸራረፈ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ

4.    በማንኛውም ግዳጅ/ ሁኔታ የላቀ ውጤት

 

 

 

Connect with us!

  • Facebook: defence
  • Flickr: defence
  • Twitter: defence
  • YouTube: defence
Copyright © 2012. Ministry of National Defence. Designed by fdredefenceforce.gov.et